Author: Abay (Administrator )

ዓባይ ባንክ በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ባለው የትንሣዔ ባዛር ለደንበኞች የተሟላ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል
Post

ዓባይ ባንክ በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ባለው የትንሣዔ ባዛር ለደንበኞች የተሟላ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል

ዓባይ ባንክ የ2015 ዓ.ም የትንሣዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በሚሊኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው ባዛር ላይ በመሳተፍ ለጎብኝዎችና ለተሳታፊዎች በባዛሩ ላይ የሚያስፈልጋቸውን ማንኛውም የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ የባዛሩ ታዳሚ ደንበኞች የሚያስፈልጋቸውን የባንክ አገልግሎቱን በመጠቀም ላይ ይገኛሉ፡፡ መጥተው እንዲጎበኙን ጋብዘንዎታል፡፡  ዓባይ ባንክ ለደንበኞች አመቺ በሆኑ ጊዜ እና ቦታዎች ላይ በመገኘት ዘርፈ ብዙ የባንክ አገልግሎትን በመስጠት ላይ ሲሆን÷...

ዓባይ ባንክ በኤግዚቢሽን ማዕከል የትንሣዔ ባዛር ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል
Post

ዓባይ ባንክ በኤግዚቢሽን ማዕከል የትንሣዔ ባዛር ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል

ዓባይ ባንክ የ2015 ዓ.ም የትንሣዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በተዘጋጀው ባዛር ላይ በመሳተፍ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ባንካችን ለጎብኝዎችና ለተሳታፊዎች በባዛሩ ላይ የሚያስፈልጋቸውን ማንኛውም የባንክ አገልግሎቶች በመስጠት ላይ ሲሆን መጥተው እንዲጎበኙን ጋብዘንዎታል፡፡በሴንቸሪ ፕሮሞሽን “ሰላም ፋሲካ-ኤክስፖ 2023” በሚል ተዘጋጅቶ በደማቅ ሁኔታ የተከፈተው ባዛር እስከ ሚያዚያ 07/2015 ዓ.ም ለጎብኝዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡

ዓባይ ባንክ እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ
Post

ዓባይ ባንክ እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ

ዓባይ ባንክ አ.ማ እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የውል ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል፡፡ስምምነቱን የዓባይ ባንክ የባሕር ዳር ቀጠና ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ሲሳይ ጸጋዬ እና የአሚኮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ሰጥዬ ተፈራርመዋል፡፡ስምምነቱ የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ሠራተኞች የቤትና የመኪና መግዣ እንዲሁም ለተለያዩ ጉዳዮች የሚያስፈልጋቸውን ብድር ከባንኩ እንዲያገኙ የሚያስችል ይሆናል፡፡ዓባይ ባንክ አገልግሎቱን በመስፋፋት ደንበኞቹን...

እንኳን ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን አደረስዎ!
Post

እንኳን ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን አደረስዎ!

ዓባይ ባንክ አ.ማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚከበረው የሴቶች ቀን እንኳን በሰላም አደረስዎ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡ ዓባይ ባንክ የሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው አገር አቀፍ ጥረት የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ሴቶችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ የባንክ አገልግሎቶችን በማቅረብ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

ዓባይ ባንክ ለባሕር ዳር መሰናዶ ትምህር ቤት ድጋፍ አደረገ
Post

ዓባይ ባንክ ለባሕር ዳር መሰናዶ ትምህር ቤት ድጋፍ አደረገ

ዓባይ ባንክ አ.ማ በባሕር ዳር መሰናዶ ትምህርት ቤት የሴት ተማሪዎች መጸዳጃ ቤት፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ውሃ ማጣሪያ ግንባታ አሰርቶ ለትምህርት ቤቱ አስረከበ፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የባንኩ የባሕር ዳር ቀጠና ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ጸጋዬ ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የተለያዩ ስራዎችን በስፋት እየሰራ መሆኑን አንስተው÷ በባሕር ዳር መሰናዶ ትምህርት ቤት የተደረገውም ግንባታ የዚሁ...

ዓባይ ባንክ ለ6ኛ ዙር ያዘጋጀው የይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ ፕሮግራም አሸናፊዎች ሽልማት አስረከበ
Post

ዓባይ ባንክ ለ6ኛ ዙር ያዘጋጀው የይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ ፕሮግራም አሸናፊዎች ሽልማት አስረከበ

ዓባይ ባንክ አ.ማ የ6ኛ ዙር “የይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” ፕሮግራም አሸናፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ስነ ስርዓት  የካቲት 17/2015 ዓ.ም በኃይሌ ግራድ አዲስ አበባ ሆቴል አከናውኗል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ የኃላ ገሠሠ የፕሮግራሙ  ዋና አላማ የደንበኞችን የቁጠባ ባህል ለማጎልበትና በባንኩ የውጭ ምንዛሬ አገልግሎት በመጠቀም ህጋዊ የገንዘብ ምንዛሬን ለማበረታታት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ባንኩ በአሁኑ ሰዓት...

የዓባይ ባንክ የስራ አመራርና ሠራተኞች ደም ለገሱ
Post

የዓባይ ባንክ የስራ አመራርና ሠራተኞች ደም ለገሱ

የዓባይ ባንክ አ.ማ.  ተቋማዊ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በበርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እየተሳተፈ  የሚገኝ ሲሆን፣ ይህን ተሳትፎውን ይበልጥ ለማጎልበት የባንኩ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች  በባንኩ ዋና መ/ቤት  በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች እንዲውል ለብሄራዊ የደም ባንክ አገልግሎት የደም ልገሳ  አካሂደል፡፡ ዓባይ ባንክ ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት እንዲቻል ለወገኖችና ተቋማት ትርጉም ያለው ድጋፍ በማድረግና ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ...

የዓባይ ባንክ የ“ይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” ፕሮግራም የዕጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት ተካሄደ
Post

የዓባይ ባንክ የ“ይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” ፕሮግራም የዕጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት ተካሄደ

ዓባይ ባንክ ከነሐሴ 26/2014 ዓ.ም እስከ ጥር 19/2015 ዓ.ም ድረስ ሲያከናውን የቆየው “ይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” ፕሮግራም የዕጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ በዕጣ አወጣጡ ሥነ ሥርዓት ላይ አቶ ወንድይፍራው ታደሰ የዓባይ ባንክ የስትራቴጂ እና ማርኬቲንግ ዋና መኮንን እንደተናገሩት የ“ይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” ፕሮግራም የደንበኞችን የቁጠባ ባህል ለማሳደግ እንዲሁም ለሀገሪቱ...