ዓባይ ባንክ ኢትዮዳሽ ከተባለ የገንዘብ አስተላለፊ ድርጅት ጋር አብሮ መስራት የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎችን በማጠናቀቅ የሐዋላ አገልግሎት መቀበል ጀምሯል፡፡ ዓባይ ባንክ ከኢትዮዳሽ ጋር አብሮ ለመስራት ያደረገው ስምምነት ዜጎችን ኢመደበኛ በሆነው ገንዘብ የማስተላለፍ ሒደት ላይ ሊያጋጥሟቸው ከሚችሉ ሥጋቶች ለመጠበቅና ከውጭ የሚላኩ የውጭ ምንዛሬዎች መደበኛ በሆኑ የባንኩ ሐዋላ አስተላላፊ ድርጅቶች በመላክ በምንዛሬው በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አስተዋፅኦ ማበርከት መቻልን...