ዓባይ ባንክ እየሰራበት የሚገኘውን ስትራቴጂ ዕቅድ በማጠናቀቅ ከ2023/24- 2027/28 ቀጣይ አምስት ዓመታት የሚገለገልበትን ስትራቴጂ ዕቅድ ዝግጅት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መድረክ አካሂዷል፡፡ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ መድረኩን በይፋ አስጀምረዋል፡፡ አቶ የኋላ በመድረኩ እንደገለጹት ስትራቴጂ ዕቅዱ ዓባይ ባንክ ጊዜው የሚጠይቀውን የደንበኞቹን ፍላጎት በተሻለ መልክ ለሟሟላት የሚያስችል የባንክ አገልግሎቶችን ለማቅረብ እና ይበልጥ በባንክ ኢንደስትሪው...