ዓባይ ባንክ አ.ማ. እና ፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት አድርገዋል፡፡ ስምምነቱ የአገር አቋራጭ የጉዞ ትኬት ክፍያን በዓባይ ባንክ ሞባይል ባንኪንግ እንዲሁም በቅርንጫፎች በኩል በሂሳብ ወይም በጥሬ ገንዘብ መፈጸም የሚያስችል ነው፡፡ በዚህ መሰረት አገልግሎቱ መነሻውን ከአዲስ አበባ በማድረግ ወደ ባሕርዳር፣ ጎንደር፣ ደብረማርቆስ፣ ደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ጅማ፣ ነቀምቴ፣ ሚዛን ተፈሪ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ባሌ...