ተቋማዊ ፍልስፍና

ራዕያችን

የላቀ ባንክ መሆን!

ተልዕኳችን

የሰለጠነ የሰው ኃይል እና ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በማቀናጀት የተሟላ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የባለድርሻ

አካላትን ፍላጎት ለማሟላት ጥረት ማድረግ፡፡

እሴቶቻችን

  • የደንበኞችን እርካታ ማረጋገጥ፣
  • ታማኝነት፣
  • በጋራ መሥራት፣
  • ዘመናዊ አሠራርን ማስረፅ፣
  • የሠራተኞችን እርካታ ማረጋገጥ፣
  • ማኅበራዊ ኃላፊነትን መወጣት፡፡

መርሃችን

ዓባይ -ታማኝ አገልጋይ!

የባንኩ አመራርና አስተዳደር

ዓባይ ባንክ የሚመራው በጠቅላላ ጉባዔ በተመረጡ የቦርድ አባላት ሲሆን፣ ተጠሪነታቸውም በቀጥታ ለጠቅላላ ጉባዔው ነው፡፡ የቦርዱ አመራር ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ እና ተደራሽ የባንክ አገልግሎት እንዲፈጠር በማድረግ የባለአክሲዮኖችን ጥቅም ለማሳደግ ተግቶ ይሠራል፡፡ የዓባይ ባንክ የበላይ አመራር አባላትም በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ እና በትምህርት ዝግጅታቸውም ብቁና ተወዳዳሪ ናቸው፡፡ ዓባይ ባንክ እ.ኤ.አ. እስከ ጁን 2022 ድረስ ከ3,530/ሶስት ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ/ በላይ ሠራተኞች ቀጥሮ በማሠራት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ከሁሉም በበለጠ የባንኩ አመራር እና ሠራተኞች የባንኩን ራዕይና ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነትና በትጋት ይሠራሉ፡፡