ዓባይ ባንክ አ.ማ. በዋግ ኸምራ እና በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን እርዳታ የሚውል የአስር ሚሊየን ብር ድጋፍ በዛሬው ዕለት አደረገ። ድጋፉን አቶ የኋላ ገሠሠ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ የአማራ መልሶ ማቋቋም ልማት ድርጅት (አመልድ) ዋና ዳይሬክተር አስረክበዋል፡፡ ዓባይ ባንክ በተለያዩ ጊዜያት በሀገራችን ተከስተው ለነበሩ ማኅበራዊ ቀውሶች ድጋፍ በማድረግ አጋርነቱን ሲያሳይ...