ዓባይ ባንክ አ.ማ. ከ2023/24-2027/28 የሚገለገልበትን የአምስት ዓመታት ስትራቴጂ ዕቅድ በየደረጃው የሚገኙ የባንኩ የሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በተካሄደ ዝግጅት ይፋ አደረገ። የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እንደተናገሩት ነባራዊውን የዓለምአቀፍ እና የሀገሪቱን አጠቃላይ ኢኮኖሚ ያገናዘበ፣ የባንክ ኢንዱስትሪውን ፈጣን ዕድገት ከግምት ውስጥ ያስገባ፣ የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችል፣ ተፎካካሪ እና ውጤታማ የሆነ የስትራቴጂ ዕቅድ መዘጋጀቱን...