ዓባይ ባንክ አ.ማ. ከሸገር ከተማ ፉሪ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው ዕለት በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱን አቶ አቡበከር ነዚር የዓባይ ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተጠባባቂ ምክትል ዋና መኮንን እና ዶ/ር አሚን መሐመድ አሊ የሸገር ከተማ ፉሪ ክፍለከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ ተፈራርመዋል፡፡ ...