ዓባይ ባንክ አ.ማ. የ2022/23 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አመራር አባላት ስብሰባ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የባንኩ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላት፣ የዲስትሪክት ኃላፊዎች እና ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች በተገኙበት ከሐምሌ 7 እስከ 8/2015 ዓ.ም አካሂዷል። በተመሳሳይ ሁኔታ በአዲስ አበባም በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ስብሰባው ተካሂዷል፡፡
Category: <span>ማስታወቂያ</span>
ዓባይ ባንክ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ድጋፍ አደረገ
ዓባይ ባንክ ሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ በተከናወነው ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር ላይ የስትራቴጂክ አጋር በመሆን 5,000,000.00 (አምስት ሚሊየን) ብር ድጋፍ አድርጓል። መርሐግብሩ ላይ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ መምህራን፣ ዘማሪያን፣ የኪነጥበብ ሰዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እንዲሁም የእምነቱ...
የደሴ ከተማ አስተዳደር ከዓባይ ባንክ ባገኘው የ200 ሚሊየን ብር ብድር የተገዙ የመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታ መሣሪያዎችን ተረከበ
ዓባይ ባንክ አ.ማ. የደሴ ከተማ አስተዳደር የልማት ሥራዎችን ለመደገፍ ለከተማ አሰተዳደሩ በሰጠው የ200 ሚሊየን ብር ብድር የተገዙ የመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታ መሣሪያዎች/ማሽኖች/ የከተማ አስተዳደሩ መረከቡን አስታውቋል፡፡ የዓባይ ባንክ አ.ማ. ደሴ ዲስትሪክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ ተስፋዬ የማሽኖቹ ርክክብ በተካሄደበት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት ዓባይ ባንክ ለደሴ ከተማ አስተዳደር ብድር በመስጠት የመንገድ ግንባታ ማሽኖች መግዛት ማስቻሉ ባንኩ...
ዓባይ ባንክ አዲሱን የአምስት ዓመታት ስትራቴጂ ዕቅድ ትውውቅ አካሄደ
ዓባይ ባንክ አ.ማ. ከ2023/24-2027/28 የሚገለገልበትን የአምስት ዓመታት ስትራቴጂ ዕቅድ በየደረጃው የሚገኙ የባንኩ የሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በተካሄደ ዝግጅት ይፋ አደረገ። የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እንደተናገሩት ነባራዊውን የዓለምአቀፍ እና የሀገሪቱን አጠቃላይ ኢኮኖሚ ያገናዘበ፣ የባንክ ኢንዱስትሪውን ፈጣን ዕድገት ከግምት ውስጥ ያስገባ፣ የደንበኞችን ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችል፣ ተፎካካሪ እና ውጤታማ የሆነ የስትራቴጂ ዕቅድ መዘጋጀቱን...
ዓባይ ባንክ የ3ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አመራር አባላት ስብሰባ አካሄደ
ዓባይ ባንክ አ.ማ. የ2023 3ኛ ዓመት የሥራ አመራር አባላት ስብሰባ በኃይሌ ግራንድ ሆቴል አካሂዷል። በስብሰባው ላይ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እና የባንኩ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
ዓባይ ባንክ እና አዲል ኮርፖሬት ግሩፕ የጋራ ሥራ ስምምነት ተፈራረሙ
ዓባይ ባንክ አ.ማ. ከአዲል ኮርፖሬት ግሩፕ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው ዕለት በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱን የዓባይ ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አቡበከር ነዚር እና የአዲል ኮርፖሬት ግሩፕ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አዲል አብደላ ታቢት (ፒኤችዲ) ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ ባንኩ በሚሰጠው ሰዲቅ -ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በኩል በበርካታ የፋይናንስ...
ዓባይ ባንክ 477ኛውን ቅርንጫፍ በወ/ሮ ኢትዮጵያ ታደሰ ስም በመሰየም ሥራ አስጀመረ
ዓባይ ባንክ አ.ማ. ለበርካታ ዓመታት የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ እንዲሁም የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ በቆዩት በወ/ሮ ኢትዮጵያ ታደሰ ስም የሰየመውን 477ኛ ቅርንጫፉን በአያት ጣፎ አካባቢ በመክፈት ሥራ አስጀምሯል። ወ/ሮ ኢትዮጵያ ታደሰ ዓባይ ባንክ በስማቸው ቅርንጫፍ በመሰየም ለሰጣቸው አክብሮት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዓባይ ባንክ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተደራሽነቱን በማስፋፋት ላይ ሲሆን አሁን ላይ የቅርንጫፎቹን ብዛት...
ዓባይ ባንክ ነባር የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላቱን በክብር ሸኘ
ዓባይ ባንክ አ.ማ. ባንኩን ላለፉት ዓመታት ሲያገለግሉ የነበሩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል ባዘጋጀው ዝግጅት ሽኝት አድርጓል። ባንኩን በዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢነት ሲያገለግሉ የቆዩት ወ/ሮ ኢትዮጵያ ታደሠ እና ሶስት የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ሽኝት ተደርጎላቸዋል። በኘሮግራሙ ላይ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላቱ ለባንኩ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል። የዕለቱ የክብር...
ዓባይ ባንክ በደሴ ከተማ ለተካሄደው የኢፍጣር ፕሮግራም ድጋፍ አደረገ
ዓባይ ባንክ አ.ማ. የ1444ኛውን የታላቁ የረመዳን ጾም ምክንያት በማድረግ በደሴ ከተማ በተካሄደው የኢፍጣር ፕሮግራም ድጋፍ አድርጓል፡፡በዝግጅቱ ላይ በሺህዎች የሚቆጠሩ የእምነቱ ተከታዮች የታደሙ ሲሆን ፕሮግራሙ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ባንኩ ድጋፍ በማድረግ የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ዓባይ ባንክ የኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተለያዩ ጊዜያት ለማህበረሰቡ ትርጉም ያለው የገንዘብ እና የዓይነት ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡
ዓባይ ባንክ በጉምሩክ ኮሚሽን ዕውቅና ተሰጠው
ዓባይ ባንክ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የልዩ መብት መታወቂያ የምስክር ወረቀት መጋቢት 26/2015 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተከናወነ የእውቅና አሰጣጥ ፕሮግራም ተቀብሏል፡፡ የልዩ መብት መታወቂያ የምስክር ወረቀቱን የዓባይ ባንክ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ከፍተኛ አማካሪ ወ/ሮ እመቤት ስጦታው ከገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ ተቀብለዋል፡፡ በመርሃግብሩ ባንኮች፣ ኢንሹራንሶች፣ አስመጪዎች፣ ላኪዎች፣ አምራቾች እና የጉምሩክ አስተላላፊዎች በአጠቃላይ 193 ከፍተኛ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች...