ዓባይ ባንክ አ.ማ. የ1444ኛውን የታላቁ የረመዳን ጾም ምክንያት በማድረግ በደሴ ከተማ በተካሄደው የኢፍጣር ፕሮግራም ድጋፍ አድርጓል፡፡በዝግጅቱ ላይ በሺህዎች የሚቆጠሩ የእምነቱ ተከታዮች የታደሙ ሲሆን ፕሮግራሙ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ባንኩ ድጋፍ በማድረግ የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ዓባይ ባንክ የኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተለያዩ ጊዜያት ለማህበረሰቡ ትርጉም ያለው የገንዘብ እና የዓይነት ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡
Category: <span>ዜና</span>
ዓባይ ባንክ በጉምሩክ ኮሚሽን ዕውቅና ተሰጠው
ዓባይ ባንክ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የልዩ መብት መታወቂያ የምስክር ወረቀት መጋቢት 26/2015 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተከናወነ የእውቅና አሰጣጥ ፕሮግራም ተቀብሏል፡፡ የልዩ መብት መታወቂያ የምስክር ወረቀቱን የዓባይ ባንክ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ከፍተኛ አማካሪ ወ/ሮ እመቤት ስጦታው ከገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ ተቀብለዋል፡፡ በመርሃግብሩ ባንኮች፣ ኢንሹራንሶች፣ አስመጪዎች፣ ላኪዎች፣ አምራቾች እና የጉምሩክ አስተላላፊዎች በአጠቃላይ 193 ከፍተኛ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች...
ዓባይ ባንክ በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ባለው የትንሣዔ ባዛር ለደንበኞች የተሟላ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል
ዓባይ ባንክ የ2015 ዓ.ም የትንሣዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በሚሊኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው ባዛር ላይ በመሳተፍ ለጎብኝዎችና ለተሳታፊዎች በባዛሩ ላይ የሚያስፈልጋቸውን ማንኛውም የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ የባዛሩ ታዳሚ ደንበኞች የሚያስፈልጋቸውን የባንክ አገልግሎቱን በመጠቀም ላይ ይገኛሉ፡፡ መጥተው እንዲጎበኙን ጋብዘንዎታል፡፡ ዓባይ ባንክ ለደንበኞች አመቺ በሆኑ ጊዜ እና ቦታዎች ላይ በመገኘት ዘርፈ ብዙ የባንክ አገልግሎትን በመስጠት ላይ ሲሆን÷...
ዓባይ ባንክ በኤግዚቢሽን ማዕከል የትንሣዔ ባዛር ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል
ዓባይ ባንክ የ2015 ዓ.ም የትንሣዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በተዘጋጀው ባዛር ላይ በመሳተፍ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ባንካችን ለጎብኝዎችና ለተሳታፊዎች በባዛሩ ላይ የሚያስፈልጋቸውን ማንኛውም የባንክ አገልግሎቶች በመስጠት ላይ ሲሆን መጥተው እንዲጎበኙን ጋብዘንዎታል፡፡በሴንቸሪ ፕሮሞሽን “ሰላም ፋሲካ-ኤክስፖ 2023” በሚል ተዘጋጅቶ በደማቅ ሁኔታ የተከፈተው ባዛር እስከ ሚያዚያ 07/2015 ዓ.ም ለጎብኝዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡
ዓባይ ባንክ እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ
ዓባይ ባንክ አ.ማ እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የውል ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል፡፡ስምምነቱን የዓባይ ባንክ የባሕር ዳር ቀጠና ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ሲሳይ ጸጋዬ እና የአሚኮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ሰጥዬ ተፈራርመዋል፡፡ስምምነቱ የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ሠራተኞች የቤትና የመኪና መግዣ እንዲሁም ለተለያዩ ጉዳዮች የሚያስፈልጋቸውን ብድር ከባንኩ እንዲያገኙ የሚያስችል ይሆናል፡፡ዓባይ ባንክ አገልግሎቱን በመስፋፋት ደንበኞቹን...
የኃዘን መግለጫ
እንኳን ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን አደረስዎ!
ዓባይ ባንክ አ.ማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚከበረው የሴቶች ቀን እንኳን በሰላም አደረስዎ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡ ዓባይ ባንክ የሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው አገር አቀፍ ጥረት የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ሴቶችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ የባንክ አገልግሎቶችን በማቅረብ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ዓባይ ባንክ ለባሕር ዳር መሰናዶ ትምህር ቤት ድጋፍ አደረገ
ዓባይ ባንክ አ.ማ በባሕር ዳር መሰናዶ ትምህርት ቤት የሴት ተማሪዎች መጸዳጃ ቤት፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ውሃ ማጣሪያ ግንባታ አሰርቶ ለትምህርት ቤቱ አስረከበ፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የባንኩ የባሕር ዳር ቀጠና ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ጸጋዬ ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የተለያዩ ስራዎችን በስፋት እየሰራ መሆኑን አንስተው÷ በባሕር ዳር መሰናዶ ትምህርት ቤት የተደረገውም ግንባታ የዚሁ...
ዓባይ ባንክ ለ6ኛ ዙር ያዘጋጀው የይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ ፕሮግራም አሸናፊዎች ሽልማት አስረከበ
ዓባይ ባንክ አ.ማ የ6ኛ ዙር “የይቆጥቡ፣ ይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ” ፕሮግራም አሸናፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ስነ ስርዓት የካቲት 17/2015 ዓ.ም በኃይሌ ግራድ አዲስ አበባ ሆቴል አከናውኗል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ የኃላ ገሠሠ የፕሮግራሙ ዋና አላማ የደንበኞችን የቁጠባ ባህል ለማጎልበትና በባንኩ የውጭ ምንዛሬ አገልግሎት በመጠቀም ህጋዊ የገንዘብ ምንዛሬን ለማበረታታት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ባንኩ በአሁኑ ሰዓት...
የዓባይ ባንክ የስራ አመራርና ሠራተኞች ደም ለገሱ
የዓባይ ባንክ አ.ማ. ተቋማዊ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በበርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህን ተሳትፎውን ይበልጥ ለማጎልበት የባንኩ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በባንኩ ዋና መ/ቤት በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች እንዲውል ለብሄራዊ የደም ባንክ አገልግሎት የደም ልገሳ አካሂደል፡፡ ዓባይ ባንክ ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት እንዲቻል ለወገኖችና ተቋማት ትርጉም ያለው ድጋፍ በማድረግና ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ...